ፕሬዚዳንት ሙላቱ ለስምንት አምባሳደሮች ሹመት ሰጡ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 9 ፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ኢትዮጵያን በውጭ ሀገሮች ለሚወክሉ አምባሳደሮች ሹመት ሰጡ።
ፕሬዚዳንቱ በዛሬው እለት ነው ለስምንት አምባሳደሮች የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት የሰጡት።
የባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ሹመት የተሰጣቸው፥ አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ፣ አቶ ቶሎሳ ሻጊ፣ አቶ ፀጋዬ በርሄ፣ አቶ ረጋሳ ከፍአለ፣ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ፣ አምባሳደር አብዱልአዚዝ አህመድ እና አቶ ግርማ ተመስገን ናቸው።
መረጃውን ያደረሰን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው።